የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በቅርቡ ጆሃንስበርግ የገቡት 153 ፍልስጤማውያን ሁኔታ 'አጠራጣሪ' ነው አሉ
20:14 17.11.2025 (የተሻሻለ: 20:24 17.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በቅርቡ ጆሃንስበርግ የገቡት 153 ፍልስጤማውያን ሁኔታ 'አጠራጣሪ' ነው አሉ
ሮናልድ ላሞላ ሁኔታው "ፍልስጤማውያንን ከጋዛ እና ከዌስት ባንክ ለማጽዳት" እና ወደ ተለያዩ የዓለም ክፍሎች ለማስወጣት የታቀደ "በግልጽ የተቀናበረ ዘመቻ" ነው የሚወክለው፤ ደቡብ አፍሪካም ይህንን እንደምትቃወም ገልጸዋል።
ቡድኑ ባለፈው ሐሙስ ዕለት ጆሃንስበርግ የደረሰ ሲሆን፣ የእስራኤል መውጫ ማኅተም አልነበራቸውም። በድንበር ፖሊስ አማካኝነት ለ12 ሠዓታት በአውሮፕላኑ ውስጥ የቆዩ ሲሆን፣ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ወደ አገሪቱ እንዲገቡ የ90 ቀናት መደበኛ ቪዛ ፈቅደውላቸዋል።
ፍልስጤማውያንን እየረዳ ያለው "ጊፍት ኦፍ ዘ ጊቨርስ" የተሰኘው የበጎ አድራጎት ድርጅት እንደገለጸው፣ 176 ፍልስጤማውያንን የጫነ የመጀመሪያው አውሮፕላን ጥቅምት 18 /2018 ዓ.ም ደቡብ አፍሪካ ደርሷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X