በአዲስ አበባ እንጀራ እና ዳቦ በሸቀጣ ሸቀጦች ሱቅ ውስጥ እንዳይሸጡ ታገደ
19:34 17.11.2025 (የተሻሻለ: 19:44 17.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በአዲስ አበባ እንጀራ እና ዳቦ በሸቀጣ ሸቀጦች ሱቅ ውስጥ እንዳይሸጡ ታገደ
የተለያዩ ሸቀጣ ሸቀጦች በሚሸጡባቸው ሱቆች ውስጥ እንጀራ መሸጥ መከልከሉን የአዲስ አበባ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ለአገር ውስጥ ሚዲያ አሳውቋል።
ሚዲያው ዋቢ ያደረጋቸው የባለሥልጣኑ ምክትል ሥራ አስኪያጅ እንጋ እርቀታ፣ “የተለያዩ መርዛማ ነገሮች ሳሙና እና ለጤና ጠንቅ የሆኑ ሸቀጦች በሚሸጡባቸው ሱቆች በቀጥታ ለምግብነት የሚውሉትን እንጀራ እና ዳቦን መሸጥ ልክ ባለመሆኑ ለመከልከል መገደዳቸውን” ተናግረዋል።
እንጀራ እና ዳቦ መሸጥ ያለባቸው በምግብ ቤቶች፣ በዳቦ ቤተች እና በባልትና ወይም ለዚሁ መሻጫነት በተፈቀደ ቦታ ብቻ መሆኑንም አስረድተዋል።
ያልተፈቀደላቸው ነጋዴዎችም ሲሸጡ ከተገኙ አስፈላጊው የእርምት እርምጃ እንደሚወሰድባቸውም ተገለጿል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X