የካሪቢያን እና የአፍሪካ አገራት እንግሊዝ ለባሪያ ንግድ ተጠያቂ እንድትሆን ጠየቁ
18:35 17.11.2025 (የተሻሻለ: 18:44 17.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የካሪቢያን እና የአፍሪካ አገራት እንግሊዝ ለባሪያ ንግድ ተጠያቂ እንድትሆን ጠየቁ
የካሪቢያን ማኅበረሰብ ካሳ ኮሚሽን ልዑካን ቡድን (ካሪኮም) ከሰኞ እስከ ሐሙስ ድረስ ለከፍተኛ ደረጃ ስትራቴጂካዊ የማግባባት ተልዕኮ በለንደን ይገኛል።
ይህ ጉብኝት የካሪኮም 15 አባል አገራት እና የአፍሪካ ሕብረት ፍትሕን የማስፈን ጥረት እንዲፋጠን ጥሪ ባደረጉበት ወቅት የተካሄደ ነው።
ከ15ኛው እስከ 19ኛው ክፍለ ዘመን ባለው ጊዜ ውስጥ፣ ከ12.5 ሚሊዮን በላይ አፍሪካውያን ታፍነውና ተገድደው የተወሰዱ ሲሆን፣ ከ3 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት በብሪታንያ መርከቦች ወደ ካሪቢያን ተግዘዋል። በግዴታ የተሰደዱት አፍሪካውያን ያልተመለሱ የእኩልነት እና ሌሎች ጥያቄዎች ዛሬም ድረስ በጣም እውነተኛ ሆነው ቀጥለዋል።
ካሪኮም ለማሳካት ያቀዳቸው ጉዳዩች የሚከተሉትን ያካትታል፦
🟠 መደበኛ ይቅርታ፣
🟠 የገንዘብ ካሳ ፣
🟠 የትምህርት መረሃ ግብሮች እና
🟠 ለአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ መስጠት ይገኙበታል።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለጸገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X