በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ የመዳብ ማዕድን ማውጫ አካባቢ ድልድይ ተደርምሶ ቢያንስ 32 ሰዎች ሞቱ

ሰብስክራይብ

በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ የመዳብ ማዕድን ማውጫ አካባቢ ድልድይ ተደርምሶ ቢያንስ 32 ሰዎች ሞቱ

የክልሉ የውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ሮይ ካውንባ ማዮንዴ እንደተናገሩት፣ አደጋው የተከሰተው ሕገ-ወጥ ማዕድን ቆፋሪዎች በችኮላ ጊዜያዊውን ድልድይ ለመሻገር በመሞከራቸው ሲሆን ድልድዩ ተደርምሶ በጎርፍ ወደተሞላ ጉድጓድ ውስጥ ወድቋል፡፡

ሚኒስትሩ አክለውም፣ በማዕድን ማውጫው አካባቢ በሚጥለው ከባድ ዝናብ እና የመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት ጥብቅ እገዳ ቢጣልም ሕገ-ወጥ አውጪዎቹ በኃይል ወደ ስፍራው ገብተዋል። ማዩንዴ ለደረሰው አደጋ ተጠያቂ የሆኑትን ለመለየት ምርመራ መጀመሩን አረጋግጠዋል።

የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን በካላንዶ ማዕድን ማውጫ በተከሰተው ድንገተኛ አደጋ የሟቾች ቁጥር እስከ 70 ሊደርስ እንደሚችል የዘገቡ ሲሆን፣ ብዛት ያላቸው ሠራተኞች በፍርስራሽ ውስጥ ሊኖሩ ይችላሉ በሚል ስጋት የነፍስ አደን እና የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች ሕይወት የማዳን ፍለጋቸውን ቀጥለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0