በደቡብ ምሥራቅ እንግሊዝ ምስራቅ ሰሴክስ የስደተኞች ካምፕ እቅድን የተቃወሙ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰልፈኞች 'ስታርመር ስልጣን ይልቀቁ!' ሲሉ ድምፃቸውን አሰሙ

ሰብስክራይብ

በደቡብ ምሥራቅ እንግሊዝ ምስራቅ ሰሴክስ የስደተኞች ካምፕ እቅድን የተቃወሙ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰልፈኞች 'ስታርመር ስልጣን ይልቀቁ!' ሲሉ ድምፃቸውን አሰሙ

መንግሥት 600 ወንድ ስደተኞችን በአቅራቢያ በሚገኝ ወታደራዊ ካምፕ ለማስፈር ማቀዱ ቁጣና የደህንነት ስጋት መቀስቀሱን ተክትሎ፤ በምስራቅ ሰሴክስ ክሮቦሮው ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተቃውሟቸውን ለማሰማት አደባባይ ወጥተዋል።

ከልጆቻቸው ጋር ሰልፍ የወጡ የአካባቢው ነዋሪዎች፤ “ስታርመር ይነሳ” እያሉ ድምፃቸውን በማሰማት፤ ለሕጋዊ እርምጃ ከ12 ሺ ፓውንድ በላይ (16 ሺህ ዶላር ያህል) ላሰባሰበው ክሮቦሮው ሺልድ  የተቃውሞ በድን ድጋፋቸውን ሰጥተዋል። አዘጋጆች የጦር መሳሪያ ማሰልጠኛ ማዕከል አጠገብ የሚገኝው የስደተኞች ጣቢያ ደህንነቱ የተጠበቀ አይደለም፣ አስቤስቶስ ኬሚካል እና አነስተኛ የውሃ አቅርቦት እንዲሁም መሰል ችግሮች ያሉበት ነው ይላሉ። ነዋሪዎች በበኩላቸው የሀገር ውስጥ ጉዳይ መሥሪያ ቤትን በተለጣፊነት እና ኃላፊነትን ባለመወጣት ከሰዋል።

ተጨማሪ የተቃውሞ ሰልፍ በሚቀጥለው ሳምንት መጨረሻ ለማካሄድ ታቅዷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበደቡብ ምሥራቅ እንግሊዝ ምስራቅ ሰሴክስ የስደተኞች ካምፕ እቅድን የተቃወሙ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰልፈኞች 'ስታርመር ስልጣን ይልቀቁ!' ሲሉ ድምፃቸውን አሰሙ
በደቡብ ምሥራቅ እንግሊዝ ምስራቅ ሰሴክስ የስደተኞች ካምፕ እቅድን የተቃወሙ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰልፈኞች 'ስታርመር ስልጣን ይልቀቁ!' ሲሉ ድምፃቸውን አሰሙ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 16.11.2025
አዳዲስ ዜናዎች
0