የዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል የማስፋፊያ ግንባታ ተጠናቆ በይፋ ስራ ጀመረ
15:37 16.11.2025 (የተሻሻለ: 15:44 16.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል የማስፋፊያ ግንባታ ተጠናቆ በይፋ ስራ ጀመረ
ማዕከሉ የራሱ ኦክስጂን ማምረቻ ጨምሮ የህክምናው ዘርፍ በደረሰበት ዘመናዊ የህክምና መሳሪያዎች የተደራጀ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል።
የተስፋፋው የህክምና ማዕከል፦
በ1 ሺህ 800 ካ.ሜ ስፋት ላይ አርፏል።
ባለ 10 ወለል ህንፃ ነው።
320 የተኝቶ ታካሚዎች አልጋ አለው።
ማስፋፊያው ላለፉት 91 ዓመታት የነበረውን የዘውዲቱ ሆስፒታል የህክምና አገልግሎት በእጥፍ በማሳደግ፤ አዲስ አበባን የሜዲካል ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ለተጀመረው ሥራ አቅም እንደሚፈጥር አመልክተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X