ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና የኤም23 ታጣቂዎች የተኩስ አቁም ማዕቀፍ ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተዘገበ
17:53 15.11.2025 (የተሻሻለ: 18:04 15.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና የኤም23 ታጣቂዎች የተኩስ አቁም ማዕቀፍ ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተዘገበ
የዶሃ ሁሉን አቀፍ የሰላም ስምምነት ማዕቀፍ የተኩስ አቁም ስምምነት በዛሬው ዕለት ዶሃ ውስጥ መፈረሙን የምዕራቡ ዓለም የዜና አውታር ዘግቧል።
የኳታር ዋና አደራዳሪ ሞሐመድ አል-ኹለይፊ፤ አሸማጋይ ወገኖች በቦታው ሰላምን ለማስፈን ጥረታቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ። ስምምነቱን "ታሪካዊ" ሲሉም ገልፀውታል።
ኮንጎ እና የኤም23 አማፂ ቡድን በሐምሌ ወር ኳታር ውስጥ የተኩስ አቁም ስምምነት እና የማዕቀፍ ስምምነት ተፈራርመው ነበር። ሆኖም ሁለቱም ወገኖች ተኩስ አቁሙን ባለማክበር ተከሰው የስምምነት ጥሰት ተመዝግቧል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X