ናሚቢያ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል አማፂ ቡድንን የጅምላ ጭፍጨፋ በማውገዝ፤ በሱዳን ዳርፉር የዘር ማጥፋት እንዳይፈፀም አስጠነቀቀች
20:12 14.11.2025 (የተሻሻለ: 20:14 14.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ናሚቢያ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል አማፂ ቡድንን የጅምላ ጭፍጨፋ በማውገዝ፤ በሱዳን ዳርፉር የዘር ማጥፋት እንዳይፈፀም አስጠነቀቀች
የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አማፂ ቡድኑ የዳርፉር ክልልን መቆጣጠሩን ተከትሎ "የጅምላ ግድያ"፣ "የዘር ማጥፋት" እና "የሰብዓዊ እርዳታ እጦት" አስመልክቶ የሚወጡ ዘገባዎች እንዳሳሰቡት ገልጿል፡፡
ፈጠኖ ደራሽ ኃይሉ የሰሜን ዳርፉር ዋና ከተማ ኤል-ፋሽርን ከተቆጣጠረ በኋላ የተባበሩት መንግሥታት እና የአፍሪካ ኅብርት የጅምላ ጭፍጨፋ እና ረሃብ በሱዳን ሊከሰት ይቸላል ሲሉ ማስጠንቀቃቸውን ተከትሎ መግለጫውን እንዳወጣ አመልክቷል፡፡
ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ አስቸኳይ የሰብዓዊ ኮሪዶር አስፈላጊነት እና የዓለም አቀፍ ሕግ መከበር ላይ አፅንኦት ሰጥቷል፡፡
ናሚቢያ "አስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ፣ የጥይት ድምፅ እንዳይሰማ፤ በሱዳን እና በመላው አፍሪካ ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ ጥሪዋን በድጋሚ ታቀርባለች” ሲል መግለጫው አጠቃሏል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X