የትራምፕ አስተዳደር በርካታ ዩክሬናውያንን ከሀገር ሊያስወጣ እየተዘጋጀ ነው ተባለ
15:35 14.11.2025 (የተሻሻለ: 15:44 14.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የትራምፕ አስተዳደር በርካታ ዩክሬናውያንን ከሀገር ሊያስወጣ እየተዘጋጀ ነው ተባለ
በአሜሪካ የዩክሬን አምባሳደር 80 ያህል ዜጎች በተለያዩ የሕግ ጥሰቶች ምክንያት ከሀገር ሊባረሩ እንደሆነ መናገራቸውን መገናኛ ብዙኃን ዘግቧል።
እንደ ህትመቱ ከሆነ አንዳንዶቹ በወታደራዊ በረራ ወደ ዩክሬን ወይም ፖላንድ እንደሚጓዙ ተነግሯቸዋል።
ሪፖርቱ እንደሚያመለክተው ሊባረሩ የሚችሉ ተብለው የተለዩ ሰዎች ወደ ግንባር ሊላኩ ይችላሉ የሚል ስጋት እንዳላቸው የወከሏቸው ጠበቆች ተናግረዋል።
"አሜሪካ የፈለገችውን ያህል ብታባርር፤ እኛ በጥሩ ሁኔታ እንጠቀምባቸዋለን" ሲሉ የዘለንስኪ አማካሪ ለጋዜጣው ተናግረዋል፡፡
ዩክሬን በጦር ግንባር ላይ ብዙ የሰው ኃይል ስለሚያስፈልጋት ዜጎቿን ከአውሮፓ ሀገራት ለመመለስ ለአዳዲስ ቅስቀሳዎች እና እርምጃዎች እየተዘጋጀች ነው ሲሉ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማርያ ዛካሮቫ ዛሬ ተናግረዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X