ቢቢሲ ለትራምፕ ይቅርታ አቀረበ፤ ሆኖም ካሳ እንደማይከፍል አስታውቋል
13:38 14.11.2025 (የተሻሻለ: 13:44 14.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ቢቢሲ ለትራምፕ ይቅርታ አቀረበ፤ ሆኖም ካሳ እንደማይከፍል አስታውቋል
የመገናኛ ብዙኃኑ ሊቀመንበር ሳሚር ሻህ፤ ዶናልድ ትራምፕ በታህሳስ 28፣ 2013 ዓ.ም ያደረጉትን ንግግር አዛብቶ በማሠራጨቱ ለፕሬዝዳንቱ በግል ይቅርታ መላካቸውን ተቋሙ ባወጣው መግለጫ አስታወቋል፡፡
በተመሳሳይ በጉዳዩ ላይ ከስም ማጥፋት ጋር ተያይዞ የሚነሱ የሕግ ጥያቄዎችን እንደማይቀበል እና የትራምፕን መግለጫ መሠረተ ቢስ ሲል ገልጿል፡፡
ቀደም ሲል ቢቢሲ በ2024 በለቀቀው የተቀነባበረ ዘጋቢ ፊልም፤ ትራምፕ በካፒቶል የዓመፅ ጥሪ እንደቀሰቀሱ አድርጎ አቅርቧል መባሉን ተከትሎ በተፈጠረው ፍጭት የቢቢሲ ዋና ዳይሬክተር እና ሥራ አስፈጻሚ ሥራቸውን ለቀዋል፡፡
የትራምፕ አስተዳደር ይፋዊ ይቅርታ እንደሚፈልግ አልያም የ1 ቢሊዮን ዶላር ክስ እንደሚያቀርብ ገልጾ ነበር፡፡
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ ቢቢሲ የትራምፕን ንግግር በተሳሳተ ሁኔታ አቀነባብሮ ማቅረቡን 'አስነዋሪ ወንጀል' ነው ሲሉ ገልፀውታል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X