የሩሲያ እና የካዛክስታን ፕሬዝዳንቶች የስትራቴጂያዊ አጋርነት መግለጫን አፀደቁ

ሰብስክራይብ

የሩሲያ እና የካዛክስታን ፕሬዝዳንቶች የስትራቴጂያዊ አጋርነት መግለጫን አፀደቁ

ሰነዱ በክሬምሊን የተደረገውን ውይይት መጠናቀቅ ተከትሎ በዛሬው ዕለት ተፈርሟል።

የሰነዱ ቁልፍ ሃሳቦች፦

🟠 እንደ ፑቲን ገለጻ፣ ውይይቶቹ ገንቢ እና ፍሬያማ ነበሩ።

🟠 ሞስኮ እና አስታና በህዋ እና በኃይል ዘርፎች ትብብራቸውን እያሰፉ ሲሆን የነዳጅ ምርቶችንም ይለዋወጣሉ።

🟠 ጋዝፕሮም በተለይ ወደ ሰሜናዊ እና ምስራቃዊ ካዛክስታን የሚላኩትን ምርቶች ለመጨመር ዕድሎችን እየፈለገ ነው።

🟠 በኬሚካል ኢንዱስትሪ እና ብርቅዬ የምድር ማዕድናትን ማውጣት ላይ የሚደረጉ ትብብሮችን ለማሻሻል የሚያስችሉ ዕቅዶችን ውይይት እየተደረገባቸው ነው።

🟠 የካዛኪስታን ፕሬዝዳንት ቶካዬቭ እንደ ገለጹት፣ የሻንጋይ የትብብር አገሮች፣ "የኮመንዌልዝ" እና ገለልተኛ አገራት እንዲሁም የደህንነትና የትብብር ስምምነት ድርጅት እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ውስጥ ቅንጅት ማጠናከርን በተመለከተ ተወያይተዋል።

🟠 ቶካዬቭ በተለይ በካዛክስታን የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ለመገንባት በሚደረገው ፕሮጀክት ላይ ከሮሳቶም ጋር ያለውን ፍሬያማ ትብብር አጉልተው ገልፀዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0