የሩሲያ እና የካዛክስታን ፕሬዝዳንቶች የስትራቴጂያዊ አጋርነት መግለጫን አፀደቁ
20:47 12.11.2025 (የተሻሻለ: 20:54 12.11.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ እና የካዛክስታን ፕሬዝዳንቶች የስትራቴጂያዊ አጋርነት መግለጫን አፀደቁ
ሰነዱ በክሬምሊን የተደረገውን ውይይት መጠናቀቅ ተከትሎ በዛሬው ዕለት ተፈርሟል።
የሰነዱ ቁልፍ ሃሳቦች፦
🟠 እንደ ፑቲን ገለጻ፣ ውይይቶቹ ገንቢ እና ፍሬያማ ነበሩ።
🟠 ሞስኮ እና አስታና በህዋ እና በኃይል ዘርፎች ትብብራቸውን እያሰፉ ሲሆን የነዳጅ ምርቶችንም ይለዋወጣሉ።
🟠 ጋዝፕሮም በተለይ ወደ ሰሜናዊ እና ምስራቃዊ ካዛክስታን የሚላኩትን ምርቶች ለመጨመር ዕድሎችን እየፈለገ ነው።
🟠 በኬሚካል ኢንዱስትሪ እና ብርቅዬ የምድር ማዕድናትን ማውጣት ላይ የሚደረጉ ትብብሮችን ለማሻሻል የሚያስችሉ ዕቅዶችን ውይይት እየተደረገባቸው ነው።
🟠 የካዛኪስታን ፕሬዝዳንት ቶካዬቭ እንደ ገለጹት፣ የሻንጋይ የትብብር አገሮች፣ "የኮመንዌልዝ" እና ገለልተኛ አገራት እንዲሁም የደህንነትና የትብብር ስምምነት ድርጅት እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ውስጥ ቅንጅት ማጠናከርን በተመለከተ ተወያይተዋል።
🟠 ቶካዬቭ በተለይ በካዛክስታን የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ለመገንባት በሚደረገው ፕሮጀክት ላይ ከሮሳቶም ጋር ያለውን ፍሬያማ ትብብር አጉልተው ገልፀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X