ሞስኮ በደቡብ ሱዳን ላይ የተጣለው የጦር መሳሪያ እገዳ እንዲነሳ 'ያለማቋረጥ' እየተሟገተች ነው ሲሉ በተመድ የሩሲያ ምክትል መልዕክተኛ ተናገሩ

ሞስኮ በደቡብ ሱዳን ላይ የተጣለው የጦር መሳሪያ እገዳ እንዲነሳ 'ያለማቋረጥ' እየተሟገተች ነው ሲሉ በተመድ የሩሲያ ምክትል መልዕክተኛ ተናገሩ
"በደቡብ ሱዳን ላይ የተጣለው የጦር መሳሪያ እገዳ ጎጂነት እንዳለው ዳግም እናረጋግጣለን" ሲሉ አና ዬቭስቲግኔዬቫ በተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ተናግረዋል።
እገዳውን አስመልክተው በአጽንኦት እንዳስረዱት፣ "በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ያሉ የአፍሪካ ተወካዮች ጭምር እገዳው እንዲገመገም ወይም እንዲላላ የጠየቁት፣ የተዋሃደ ጦር ለመመስረትና ለማስታጠቅ ዋነኛው እንቅፋት በመሆኑ ነው" ብለዋል።
እየተጋረጡ ያሉትን የደህንነት ተግዳሮቶችን ለመቋቋም ከእገዳ ውጭ ያሉት እንቅስቃሴዎች "በቂ አለመሆናቸውን" ጠቁመው፣ ሩሲያ "እገዳው እንዲላላ ብሎም ሙሉ በሙሉ እንዲነሳ ያለማቋረጥ ትሟገታለች" ሲሉ አክለዋል።
እገዳው የተጣለው እ.ኤ.አ. በ2018 ነው። ባለፈው ግንቦት የፀጥታው ምክር ቤት እገዳውን ለአንድ ዓመት ያራዘመ ሲሆን፣ ሩሲያ እና ቻይናን ጨምሮ ስድስት ሀገራት ድምፅ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
በደቡብ ሱዳን ያለው ሁኔታ ባለፈው መጋቢት ላይ ተባብሶ ነበር፤ በወቅቱ በአገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል በመደበኛ ወታደሮች እና ከተቃዋሚው የሱዳን ሕዝቦች የነፃነት ንቅናቄ ጋር በተያያዙ የኋይት አርሚ ኑዌር ሚሊሻዎች መካከል ግጭት ተቀስቅሷል። መጋቢት 18፣ የንቅናቄው መሪ የሆኑት ምክትል ፕሬዝዳንቱ ሪክ ማቻር በዋና ከተማው ውስጥ በቁም እስር ስር እንዲቆዩ መደረጋቸው ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X