ሩሲያ እና ኢትዮጵያ በአስቸጋሪ ወቅቶች እርስ በርስ ሲደጋገፉ ኖረዋል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሩሲያ እና ኢትዮጵያ በአስቸጋሪ ወቅቶች እርስ በርስ ሲደጋገፉ ኖረዋል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር
ሩሲያ እና ኢትዮጵያ በአስቸጋሪ ወቅቶች እርስ በርስ ሲደጋገፉ ኖረዋል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር - Sputnik አፍሪካ, 1920, 12.11.2025
ሰብስክራይብ

ሩሲያ እና ኢትዮጵያ በአስቸጋሪ ወቅቶች እርስ በርስ ሲደጋገፉ ኖረዋል - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር

በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በሩሲያ እና ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ፣ የሳይንስ፣ የቴክኒክ ትብብርና ንግድ በይነ-መንግሥታት ኮሚሽን ጉባኤ ላይ የሀገራቱን ታሪካዊ ወዳጅነት አንፀባርቀዋል፡፡

"ታሪካዊ በሆነ መንገድ፣ ኢትዮጵያ እና ሩሲያ አስቸጋሪ ጊዜያት እርስ በእርስ ሲጠባበቁና ሲደጋገፉ ጎን ለጎን ቆመዋል የሚለው ሊታወቅ ይገባል" ሲሉ አብራርተዋል።

አክለውም በተከታታይ በከፍተኛ ባለስልጣናት የተደረጉ ጉብኝቶች፣ በአመራሮች ደረጃ የሚደረጉ ፍሬያማ ውይይቶች እና ተግባራዊ ትብብር ባህላዊ፣ ሳይንሳዊ እና ኢኮኖሚያዊ የሁለትዮሽ ግንኙነቶች እየጠነከሩ መሆናቸውን እንደሚያሳዩ አጽንኦት ሰጥተዋል።

የሩሲያ የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ማክሲም ሬሼትኒኮቭ በበኩላቸው፦

"ሁለቱ ሀገራት ለረጅም ጊዜ የዘለቀ የወዳጅነት እና የትብብር ግንኙነት አላቸው። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ደግሞ በሀገራቱ መሪዎች መካከል በተደረጉ መደበኛ ስብሰባዎች፣ በመንግሥት ደረጃ በሚደረግ ንቁ መስተጋብር እና የበይነ-መንግሥታት ኮሚሽን ሥራ ዳግም በመጀመሩ እነዚህ ግንኙነቶች ተጠናክረዋል" ብለዋል።

ሬሼትኒኮቭ አክለውም፣ የጋራ የንግድ ፍላጎት እያደገና የጋራ ፕሮጀክቶችም እየተበራከቱ መሆኑን ገልፀዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0