- Sputnik አፍሪካ, 1920
Drum of Changes
ከጥንታዊ የስልጣኔ ምድሮች እስከ ዘመናዊ ከተሞች ልብ፣ በአፍሪካ አዲስ ጥሪ እየተስተጋባ ይገኛል።አፍሪካ የዓለምን የወደፊት ሁኔታ የምትቀርጽ ቸል ልትባል የማይገባት ኃይል ሆና እያደገች ነው። ለአስርት ዓመታት አፍሪካ የምትናገር፣ ነገር ግን የማትደመጥ ሆና ቆይታለች። ዛሬ ግን ጥሪው ግልፅ ነው። አፍሪካ ከዓለም የኃይል ማዕድ የሚገባትን ትክክለኛ ቦታ ትጠይቃለች። ከአፍሪካ የሚስተጋቡ የለውጥ ድምፆችን በልካቸው ወደ አድማጭ ተመልካቾቹ ያደርሳል።

ከምዕራቡ ዓለም ባሻገር- ኢትዮጵያ ለቱሪዝሟ እድገት ወደ ደቡባዊው ዓለም ታማትራለች

ከምዕራቡ ዓለም ባሻገር- ኢትዮጵያ ለቱሪዝሟ እድገት ወደ ደቡባዊው ዓለም ታማትራለች
ሰብስክራይብ
"ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ ያለውን ሁሉ አቅፋ ይዛለች ። ስለዚህ አንድ ሰው አፍሪካን በእውነት መጎብኘት ከፈለገ፣ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ሁሉንም ማየት ይችላል።[…] ስለዚህ፣ በብሪክስ ውስጥ፣ ዓለም አቀፍ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑ አገሮችን፣ ጥሩ የህዝብ ብዛትን እና ጥሩ ኢኮኖሚን በተመሳሳይ ጊዜ እናገኛለን፤ ይህም እነርሱን የቱሪስት እንግዶቻችን ልናደርጋቸው ያስችለናል።[...] ስፑትኒክ አፍሪካ የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችን ብዙዎች ጋር ለማድረስ ይረዳናል። ሚዲያው ቢሮውን በኢትዮጵያ መክፈቱም ከራዕያችን ጋር በእጅጉ የተጣጣመ ነው" - ሲሉ የቱሪዝም ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ዝግጅታችን ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማን አነጋግሮ የኢትዮጵያ ፊቷን ወደ ሩሲያ፣ ቻይና፣ መካከለኛው ምስራቅ እና ሌሎች ሀገራት ጭምር በማዞር አዲስ የቱሪዝም የገበያ እያማተረች ስለመሆኗ ጨምሮ ሌሎች ጉዳዮችን ይዳስሳል። እንዲሁም ቻይና በቅርቡ ለአፍሪካ ሀገራት '' እተገብረዋለሁ'' ያለችውን የዜሮ ታሪፍ ጉዳይ ያነሳል። ለዚህም የፓን አፍሪካ የንግድና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት ዋና ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ ክቡር ገናን አነጋግሯል።
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ።
አዳዲስ ዜናዎች
0