የከሸፈው የሚግ-31 አውሮፕላን ጠለፋ ሩሲያና ኔቶን ለማጋጨት የታለመ በእንግሊዝ የተመራ ትንኮሳ ነበር - ባለሙያ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየከሸፈው የሚግ-31 አውሮፕላን ጠለፋ ሩሲያና ኔቶን ለማጋጨት የታለመ በእንግሊዝ የተመራ ትንኮሳ ነበር - ባለሙያ
የከሸፈው የሚግ-31 አውሮፕላን ጠለፋ ሩሲያና ኔቶን ለማጋጨት የታለመ በእንግሊዝ የተመራ ትንኮሳ ነበር - ባለሙያ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 11.11.2025
ሰብስክራይብ

የከሸፈው የሚግ-31 አውሮፕላን ጠለፋ ሩሲያና ኔቶን ለማጋጨት የታለመ በእንግሊዝ የተመራ ትንኮሳ ነበር - ባለሙያ

የፖለቲካ ተንታኝ ቫሲሊ ቤሎዜሮቭ ለስፑትኒክ እንደተናገሩት፣ የከሸፈው የጠለፋ ሴራ በኪዬቭ የሚካሄድ የ"አደጋና የሽብር ጦርነት" አካል ሲሆን፣ ኪዬቭ ደግሞ "በራሷ ተነሳሽነት ሳይሆን" ከውጭ በሚሰጥ የፖለቲካ መመሪያ እንደምትሠራ ገልጸዋል።

ይህንን አስተያየት የሰጡት የፌደራል ደኅንነት አገልግሎት (ኤፍሲቢ) የሩሲያን ሚግ-31 ተዋጊ ጄት ለመጥለፍ ያለመ የዩክሬን እና የእንግሊዝ የጋራ ኦፕሬሽን ማክሸፉን ተከትሎ የመጣ ነው።

ሞስኮ ስቴት የሥነ ልሳን ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ ትምህርት ክፍል ኃላፊ የሴራውን ዋና ዓላማዎች እንደሚከተለው ዘርዝረዋል፦

🟠 የሩሲያን ተጋላጭነት ማሳየት፣

🟠 የዩክሬንን ብቃት ማስመስከር እንዲሁም

🟠 የውስጥ አለመግባባትን አስመልክቶ የተሳሳተ ትርክት መፍጠር።

ቤሎዜሮቭ ኦፕሬሽኑን በተለየ ሁኔታ ከእንግሊዝ ጋር ያገናኙት ሲሆን፤ የሀገሪቱን የሰላም ንግግር አስመልክቶ የጥንቃቄ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። አክለውም ለንደን የምትከተለው ታሪካዊ ስትራቴጂ "ሌሎችን ተጠቅማ ጥቅሟን ማስጠበቅ" መሆኑን ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0