የአሜሪካ የነዳጅ ሀብቷን የማስጠበቅ ታሪካዊ አካሄድ 'ሌላ መልክ ያለው የቅኝ ግዛት' መቀጠሉን ያሳያል ሲሉ የቬንዙዌላ ባለሙያ ተናገሩ

የአሜሪካ የነዳጅ ሀብቷን የማስጠበቅ ታሪካዊ አካሄድ 'ሌላ መልክ ያለው የቅኝ ግዛት' መቀጠሉን ያሳያል ሲሉ የቬንዙዌላ ባለሙያ ተናገሩ
በቬንዙዌላ ማዕከላዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር እና ተመራማሪ የሆኑት አንድሬስ አንቲላኖ እንደተናገሩት፤ አሜሪካ በላቲን አሜሪካዋ ቬንዙዌላ እና አፍሪካዋ ናይጄሪያ ያላትን አቀራረብ ተመሳሳይ እንደሆነ የሚያሳዩ ግልጽ ምልክቶች አሉ።
ባለሙያው ለስፑትኒክ አፍሪካ እንደተናገሩት፤ ዋሽንግተን የገንዘብ ካፒታልን የማስፋፋት ዝንባሌዋን ሥር የሰደደ ፖሊሲ በመከተል፣ ከአንድ ምዕተ ዓመት በላይ የተረጋጋ የሃይድሮካርቦን አቅርቦትን የማረጋገጥ እርምጃ ወስዳለች።
አንቲላኖ “አሁን የምናስተውለው የቅኝ ግዛት አካሄድ በሌላ መዋቅራዊ ለውጥ መተካቱን ነው” ብለዋል።
አክለውም በአገሪቱ የተካሄደው የቦሊቫሪያን አብዮት እስኪያስተጓጉለው ድረስ ቬኔዙዌላ አስተማማኝ አቅራቢ ነበረች ሲሉ ጠቁመዋል፤ አቢዮቱ አሜሪካ ተጽዕኖዋን መልሳ ለማስመለስ ከባድ ጥረት እንድታካሂድ አድርጓል።
ተንታኙ በተመሳሳይ ሁኔታ ናይጄሪያ ላይ እየታየ ነው፤ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጧና ሀብቷ ለአሜሪካ ፍላጎት አስፈላጊ ስልታዊ አገር እንድትሆን አድርጓታል ሲሉ ይሞግታሉ።
ትራምፕ ናይጄሪያን “በተለየ ሁኔታ አሳሳቢ ሀገር” ሲሉ የሰየሟት ሲሆን፣ ተፈፅሟል ባሉት “ክርስቲያኖች ላይ የተፈፀመ የዘር ማጥፋት” ወንጀል ምክንያት ወታደራዊ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚችል ጠቁመው ነበር። ሆኖም አቡጃ የሃይማኖት ልዩነት ሳይደረግ ሁሉንም ዜጎቿን ለመጠበቅ ቁርጠኛ መሆኗን በማሳሰብ እነዚህን ክሶች በተደጋጋሚ አስተባብላለች።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X