ኢትዮጵያ ያረጁ መኪናዎችን የማስወገድ ወይም የመተካት ዕቅድ ብትይዝም የትግበራ ጊዜ አለመወሰኑን ተገለጸ
19:15 11.11.2025 (የተሻሻለ: 19:24 11.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ያረጁ መኪናዎችን የማስወገድ ወይም የመተካት ዕቅድ ብትይዝም የትግበራ ጊዜ አለመወሰኑን ተገለጸ
እርምጃው ንጹህ መጓጓዣን ለማበረታታትና በቅሪተ አካል ነዳጆች ላይ ጥገኛ መሆንን ለመቀነስ የሚደረገው ሰፊ ጥረት ጋር የተያያዘው መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታን ጠቅሶ የአገር ውስጥ የግል ሚዲያ ዘግቧል፡፡
ይህ ጉዳይ የመጨረሻ ውሳኔ እንዳልተሰጠበት እና መንግሥት የሚተኩ ወይም የሚቀየሩ መኪኖች ዕድሜ ምድቦች እየገመገመ መሆኑ ነው የተገልፀው፡፡
ተነሳሽነቱ፣ ቀጥተኛ እገዳ ሳይሆን፣ ከኢትዮጵያ የአረንጓዴ እና ዘላቂ ዕድገት ግብ ጋር ተጣጥሞ ቀስ በቀስ የሚተገበር ዕቅድ አካል መሆኑ ተሰምሮበታል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X