በማሊ በነዳጅ ቀውስ ምክንያት ለሁለት ሳምንታት ተቋርጦ የነበረው ትምህርት ዳግም ተጀመረ - የማሊ ብሔራዊ ትምህርት ሚኒስትር
16:50 11.11.2025 (የተሻሻለ: 17:14 11.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በማሊ በነዳጅ ቀውስ ምክንያት ለሁለት ሳምንታት ተቋርጦ የነበረው ትምህርት ዳግም ተጀመረ - የማሊ ብሔራዊ ትምህርት ሚኒስትር
አማዱ ሲ ሳቫኔ እንደተናገሩት፤ “የሽግግር ፕሬዝዳንቱ እና የጦር ኃይሎች ጄኔራል አሲሚ ጎይታን ጨምሮ ከፍተኛ ባለሥልጣና መስተጓጎሉን ለማለፍ እና ለአገሪቱ ቀጣይነት ያለው የነዳጅ አቅርቦት ለማረጋገጥ መሬት ላይ እየሰሩ ነው።”
ከማሊ የትምህርት ሚኒስቴር የወጣው መግለጫ እንደሚያመለክተው፣ ሚኒስትሩ የተማሪዎችን መመለስ ለመመልከት በሜዲና ኮውራ ወደሚገኘው የማማዱ ዲያራ ቁጥር 2 መሠረታዊ ትምህርት ቤት ጎብኝተዋል።
"ጃኒም" በተባለው ከአልቃይዳ* ጋር ግንኙነት ባለው ቡድን ምክንያት በተፈጠረው የነዳጅ እጥረት ሳቢያ ከጥቅምት 17 እስከ ጥቅምት 30 ድረስ በመላ አገሪቱ የትምህርት ቤት እና የዩኒቨርሲቲ ትምህርቶች ታግደው ነበር።
ባለፈው ሳምንት የማሊ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነዳጅ እጥረቱን “ሰው ሠራሽ በሆነ መንገድ የተፈጠረ ሁኔታ” ሲሉ ገልጸውታል።
*በሩሲያ ውስጥ የታገደ የሽብር ድርጅት
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia
/