ቅኝ ግዛት በመሬት ይዞታ ላይ የፈጠረውን ኢ-ፍትሐዊነት ለማረም እየሠራን ነው - የደቡብ አፍሪካ የመሬት ማሻሻያ እና የገጠር ልማት ሚኒስትር

ሰብስክራይብ

ቅኝ ግዛት በመሬት ይዞታ ላይ የፈጠረውን ኢ-ፍትሐዊነት ለማረም እየሠራን ነው - የደቡብ አፍሪካ የመሬት ማሻሻያ እና የገጠር ልማት ሚኒስትር

ቅኝ ግዛት የአፍሪካን መሬት ብቻ ሳይሆን የሕዝቦቿን ክብር መውሰዱን ሚኒስትሩ ምዝዋነሌ ነይሆጾ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

"ባርነት የነበረንን ነገር ሁሉ ወስዷል። በዚህም አሁንም ድረስ የቅኝ ግዛት ጠባሳን እየተሸከምን ነው። ነገር ግን አሁን መሬት ተገቢ ለሆኑ ባለይዞታዎች መመለሱን ለማረጋገጥ ሥራዎችን ጀመርናል።" ብለዋል።"

ምዝዋነሌ የአገሪቱ መሬትን በሕግ አግባብ ለቀድሞ ባለይዞታዎች የመመለስ ሥራ፣ ከደቡብ አፍሪካ ባለፈ የአፍሪካን ሕዝቦች ክብር እንደሚመልስም አመላክተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0