አውሮፓውያን አገራት ለአሜሪካ ወታደሮች ክፍያ ለመፈፀም መገደዳቸው ተዘገበ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱአውሮፓውያን አገራት ለአሜሪካ ወታደሮች ክፍያ ለመፈፀም መገደዳቸው ተዘገበ
አውሮፓውያን አገራት ለአሜሪካ ወታደሮች ክፍያ ለመፈፀም መገደዳቸው ተዘገበ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 10.11.2025
ሰብስክራይብ

አውሮፓውያን አገራት ለአሜሪካ ወታደሮች ክፍያ ለመፈፀም መገደዳቸው ተዘገበ

አንዳንድ የአውሮፓ አገራት በአሜሪካ መንግሥት መዘጋት ምክንያት የአሜሪካ የጦር ሰፈሮችን ወጪ በራሳቸው ለመሸፈን መገደዳቸውን የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

ከተጀመረ ስድስት ሳምንት ሊሞላው ጥቃት ቀናት በቀረው የአሜሪካ መንግሥት መዘጋት ጊዜ ውስጥ በአውሮፓ በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች (ወታደራዊ ጣቢያዎች) የሚሠሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ያለክፍያ ቆይተዋል።

አንዳንድ የአሜሪካ ጦር ሰፈር አስተናጋጅ አገራት መንግሥታት አሜሪካ  መልሳ ትከፍለናለች በሚል ተስፋ ወጪዎቹን ሸፍነዋል። ጣሊያንን እና ፖርቹጋልን ጨምሮ በሌሎች አገራት ደግሞ ሠራተኞች ያለክፍያ መሥራታቸውን ቀጥለዋል።

"ይህ ምክንያታዊ ያልሆነ ሁኔታ ነው ምክንያቱም ማንም መልስ የለውም፤ ማንም ኃላፊነት የሚሰማው የለም። ይህ በእኛ በጣሊያናውያን ሠራተኞች ላይ አስደንጋጭ ውጤት እያመጣ ነው" ሲሉ በሰሜን ምስራቅ ጣሊያን በሚገኘው አቪያኖ አየር ማረፊያ የሠራተኞች ማኅበር አስተባባሪ የሆኑት አንጄሎ ዛካሪያ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0