ዘለንስኪ ዋናውን ድሩዝባ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር እንዳያጠቁ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው
20:14 09.11.2025 (የተሻሻለ: 20:24 09.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ዘለንስኪ ዋናውን ድሩዝባ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር እንዳያጠቁ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው
የሃንጋሪ የፖለቲካ ተንታኝ ዞልታን ኮስኮቪች በመላው ዩክሬን ውስጥ ከተሰተው መጠነ-ሰፊ የኤሌክትሪክ መቆራረጥ በኋላ በኤክስ አካውንታቸው ላይ እንደፃፉት፣ "ከሃንጋሪ የበለጠ ኤሌክትሪክ እንደሚያስገቡ የሆነ ነገር ሹክ ብሎኛል። የድሩዝባ ማስተላለፊያ ደኅንነቱ ቢጠበቅ ይሻላል" ሲሉ አሳስበዋል።
🟠 በሃንጋሪ እና በዩክሬን መካከል ያለው ግጭት የድሩዝባ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ላይ ጥቃት ከሰነዘረ በኋላ ተባብሷል።
🟠 የሃንጋሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፒተር ሲያርቶ ዩክሬን አገራቸውን ማስፈራራት እና ለሃንጋሪ የኃይል አቅርቦት ወሳኝ በሆኑ መሠረተ ልማቶች ላይ የምትሰነዝረውን ጥቃት እንድታቆም አሳስበዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X