ማዳጋስካር ውስጥ መፈንቅለ መንግሥት ለመሞከር የተጠረጠሩ ሁለት የውጭ ዜጎች መታሰራቸውን ባለሥልጣኑ አስታወቁ
18:37 09.11.2025 (የተሻሻለ: 18:44 09.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ማዳጋስካር ውስጥ መፈንቅለ መንግሥት ለመሞከር የተጠረጠሩ ሁለት የውጭ ዜጎች መታሰራቸውን ባለሥልጣኑ አስታወቁ
ተጠርጣሪዎቹ በአገሪቱ ውስጥ ከአምስት ዓመት በላይ የኖሩ የንግድ ሰዎች እንደሆኑ ከፍተኛ የፖሊስ መኮንን ሩፊን ቶሎጃራ ለቢሪያ ገልጸዋል።
"ሁለቱ ተጠርጣሪዎች የውጭ ዜጎች ናቸው፤ አውሮፓውያንም ኢንዶ-ፓኪስታናውያንም አይደሉም" ሲሉም አክለዋል።
የአንደኛው ተጠርጣሪ ንብረት የሆነ ትልቅ ግቢ ሲፈተሽ 2 ቢሊዮን አርያሪ (440 ሺህ ዶላር ገደማ) ጥሬ ገንዘብ፣ የተወሰኑ የውጭ ምንዛሪ የገንዘብ ኖቶች፣ "ሦስት ኃይለኛ የአደን ጠመንጃዎች፣ እና ሦስት አውቶማቲክ ሽጉጦች" እንደተገኙ ለቢሪያ ተናግረዋል።
እነዚህ እስራት በፕሬዝዳንት ሚካኤል ራንድሪያኒሪና ላይ ቀጥተኛ ስጋትን በተመለከተ “በታማኝ መረጃ” ላይ የተመሠረተ ምርመራ አካል ናቸው።
ባለሥልጣናት እንደሚሉት፣ ከአገር ውጭ ተደራጅቷል የተባለውን የግድያ እና የመንግሥት አለመረጋጋት ሴራ ማክሸፍ ችለዋል። ሦስት ተጠርጣሪዎች ያሉት ሁለተናው ቡድን አሁንም ክትትል እየተደረገበት ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

