የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ላቭሮቭ ለስፑትኒክ የሰጡት ቁልፍ መግለጫዎች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ላቭሮቭ ለስፑትኒክ የሰጡት ቁልፍ መግለጫዎች
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ላቭሮቭ ለስፑትኒክ የሰጡት ቁልፍ መግለጫዎች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 09.11.2025
ሰብስክራይብ

 የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ላቭሮቭ ለስፑትኒክ የሰጡት ቁልፍ መግለጫዎች 

ስለ ሩሲያ እና አሜሪካ ግንኙነት፦

ሩሲያ በምትፈልገው ፍጥነት ባይሆንም በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ያለው የሩሲያ-አሜሪካ ውይይት ቀጥሏል።

የቀድሞው የአሜሪካ አስተዳደር የወረሳቸው በሩሲያ-አሜሪካ ግንኙነት ውስጥ ብዙ የሚያናድዱ ነገሮች አሉ። የሀገራቱን ግንኙነት ለማጽዳት ረጅም ጊዜ ይወስዳል።"

  ላቭሮቭ እና ሩቢዮ በየጊዜው ይነጋገራሉ እና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በአካል ለመገናኘት ዝግጁ ናቸው።

ሩሲያ በአላስካ በተካሄደው የፕሬዝዳንቶች ስብሰባ ላይ በዩክሬን ጉዳይ ላይ የተደረሱ ስምምነቶችን አሜሪካ እንድታረጋግጥ ትጠብቃለች።

ሩሲያ የስትራቴጂክ የጦር መሳሪያዎች ቅነሳ (ስታርት) ስምምነት ላይ የተቀመጡትን ገደቦች ከየካቲት 2026 በኋላ ለሌላ ዓመት ለማራዘም ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ያቀረቡትን ሐሳብ አሜሪካ እንድትቀበል ለማሳመን አላሰበችም።

"ማንም ስምምነቱን እንዲቀበል አናሳምንም። የእኛ እርምጃ ለሁለቱም ወገኖች እና ለመላው ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ጥቅም እንደሚያስገኝ እናምናለን። ለየትኛውም ሁኔታ ዝግጁ ነን።"

ስለ ዩክሬን ግጭት፦

  የዩክሬንን ግጭት የችግሩ መሠረታዊ መንስኤዎች እና የሩሲያን ጥቅሞች ግምት ውስጥ ባላስገባ መልኩ መፍታት አይቻልም።

"ክራሚያን እና ሴቫስቶፖልን በተመለከተ፣ የባሕረ ገብ መሬት ነዋሪዎች እ.ኤ.አ. በመጋቢት 2014 በተካሄደው ሕዝበ ውሳኔ የራሳቸውን ዕድል በራሳቸው የመወሰን መብት ተጠቅመው ከሩሲያ ጋር ለመዋሃድ ድምጽ ሰጥተዋል።"

  በዩክሬን ጉዳይ ላይ በሩሲያ እና በአሜሪካ መካከል የሚደረጉ ውይይቶች በአንድ ርዕስ ላይ ብቻ የተገደቡ አይደሉም፤ ስፋት ያላቸው ርዕሰ ጉዳዮችን ይሸፍናሉ።

  አሜሪካ ዘለንስኪ በዩክሬን ውስጥ ሰላማዊ መፍትሄን እንዳያደናቅፉ ለማግባባት እየተቸገረች ያለ ይመስላል።

በአውሮፓ ሕብረት የታገደው የሩሲያ ሀብት መውረስ አስመልክቶ

የታገደው የሩሲያ ሀብት በሕጋዊ መንገድ ለመውረስ የሚያስችል መንገድ የለም።

"እንዲህ ያሉ ድርጊቶች ግልጾ ማታለል እና ስርቆት ከመሆን የዘለሉ አይደሉም። የቅኝ ገዥዎችና የባሕር ወንብድ አስተሳሰቦች በአውሮፓውያን ውስጥ የነቁ (የተነሱ) ይመስላል።"

  የሩሲያ የታገደ ሀብት መወረስ ዩክሬንን አያድናትም እና ኪዬቭ እዳዎቿን እንድትከፍል አይረዳም።

  ምዕራባውያን የሩሲያን የታገደ ሀብት ለዩክሬን ካስተላለፉ፣ ሩሲያ በአግባቡ እና በምላሽ የመስጠት መርህ መሠረት ምላሽ ትሰጣለች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0