በሞስኮ የሱዳን ኤምባሲ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ለፈጥኖ ደራሽ ኃይል አማፂያን ወታደራዊ ድጋፍ እንደምታደርግ የሚያሳይ ማስረጃ አጋራ
20:38 08.11.2025 (የተሻሻለ: 20:44 08.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በሞስኮ የሱዳን ኤምባሲ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ለፈጥኖ ደራሽ ኃይል አማፂያን ወታደራዊ ድጋፍ እንደምታደርግ የሚያሳይ ማስረጃ አጋራ
ኤምባሲው የሰሜን ዳርፉር ዋና ከተማ የሆነችውን አል-ፋሽርን ቡድኑ ከተቆጣጠረ በኋላ በተፈጠሩት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ሰለባ የሆኑ ዜጎችን አስመልከቶ በተዘጋጀ መታሰቢያ ላይ እነዚህን ማስረጃዎች አሳይቷል። ከተማዋ ከ500 ቀናት በላይ በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ከበባ ስር ቆይታለች።
ማስረጃዎቹ የጦር መሳሪያዎችና የወታደራዊ ቁሳቁስ ፎቶዎችን እንዲሁም አማፂ ቡድኑ ከሱዳን መደበኛ ጦር ጋር ባደረገው ግጭት የተያዙ ተሽከርካሪዎች ውስጥ የተገኙ ሚስጥራዊ ወታደራዊ ሰነዶችን ያካተቱ ናቸው።
በመታሰቢያ ዝግጅቱ ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ በኤል-ፋሽር ሲቪል ዜጎች ላይ የፈጸማቸውን የጦር ወንጀሎች የሚያሳዩ ምስሎች ቀርበዋል። ከእነዚህም መካከል ከ450 በላይ ሲቪሎች በሆስፒታል ውስጥ በጅምላ የተገደሉበት ይገኝበታል።
እነዚህ ድርጊቶች በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ አማፂያን በቪዲዮ ተቀርፀው ማህበራዊ ሚዲያ ላይ መለጠፋቸውን፤ በሩሲያ የሱዳን አምባሳደር ሞሐመድ ሲራጅ ተናግረዋል።
የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ቡድኑን ትደግፋለች በሚል የሚቀርብባትን ክስ ውድቅ አድርጋለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

1/9
© telegram sputnik_ethiopia

2/9
© telegram sputnik_ethiopia

3/9
© telegram sputnik_ethiopia

4/9
© telegram sputnik_ethiopia

5/9
© telegram sputnik_ethiopia

6/9
© telegram sputnik_ethiopia

7/9
© telegram sputnik_ethiopia

8/9
© telegram sputnik_ethiopia

9/9
© telegram sputnik_ethiopia
1/9
© telegram sputnik_ethiopia
2/9
© telegram sputnik_ethiopia
3/9
© telegram sputnik_ethiopia
4/9
© telegram sputnik_ethiopia
5/9
© telegram sputnik_ethiopia
6/9
© telegram sputnik_ethiopia
7/9
© telegram sputnik_ethiopia
8/9
© telegram sputnik_ethiopia
9/9
© telegram sputnik_ethiopia