በኢትዮጵያ የጥቅምት ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት መጠን ቅናሽ አሳየ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበኢትዮጵያ የጥቅምት ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት መጠን ቅናሽ አሳየ
በኢትዮጵያ የጥቅምት ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት መጠን ቅናሽ አሳየ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 08.11.2025
ሰብስክራይብ

በኢትዮጵያ የጥቅምት ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት መጠን ቅናሽ አሳየ

11.7 በመቶ ሆኖ የተመዘገበው ግሽበት መጠኑ በመስከረም ወር ከነበረበት 13.2 በመቶ ዝቅ ማለቱን የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት መረጃ አመላክቷል።

ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወር ከተመዘገበው 19.3 በመቶ የዋጋ ግሽበት ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ ቅናሽ የታየበት ሆኗል።

በሪፖርቱ መሠረት፦

በወሩ የምግብ ነክ ዕቃዎች 10.2 በመቶ እንዲሁም ምግብ ነክ ያልሆኑ እቃዎች ደግሞ 14.2 በመቶ ሆነው ተመዝግበዋል።

የምግብ ነክ ያልሆኑ ዕቃዎች የዋጋ ግሽበት መጠን ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 14.2 በመቶ ከፍ ብሏል።

የታየው ቅናሽ የተሻሻለ የአቅርቦት ሁኔታዎችን እና በመመሪያ የተደገፈ የገበያ መረጋጋትን ይጠቁማል መባሉን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0