ቡርኪና ፋሶ የሽብርተኝነትን የገንዘብ ምንጭ ለመግታት በነዳጅ ማደያዎች የደህንነት ካሜራዎችን አስገዳጅ አደረገች
15:29 08.11.2025 (የተሻሻለ: 15:34 08.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ቡርኪና ፋሶ የሽብርተኝነትን የገንዘብ ምንጭ ለመግታት በነዳጅ ማደያዎች የደህንነት ካሜራዎችን አስገዳጅ አደረገች
የታጠቁ ቡድኖችን እንቅስቃሴ ለመስበር መንግሥት ከታህሳስ 23፣ 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎች የቪዲዮ ክትትል ሥርዓቶችን እንዲተክሉ ያስገድዳል።
ጥቅምት 27 የወጣ የመንግሥት አዋጅ የደህንነት ካሜራ ቀረጻዎች ቢያንስ ለሁለት ወራት እንዲቀመጡ የሚያዝ ሲሆን ባለሥልጣናትም ጥብቅ የሕግ ተገዢነት ፍተሻዎችን ያስፈጽማሉ።
የጸጥታ ሚኒስትር ማሃማዱ ሳና እርምጃው ለሽብርተኞች የሚቀርበውን የነዳጅ አቅርቦት ለመቁረጥ እንዳለመ በመግለፅ፤ በዘርፉ ትብብር ቢኖርም የማጭበርበር ድርጊቶችና ቸልተኝነት የሽብርተኞች አቅርቦቶችን በተዘዋዋሪ ማመቻቸታቸውን እንደቀጠሉ አንስተዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X