አሜሪካ ደቡብ አፍሪካ በሚካሄደው የቡድን 20 ስብሰባ እንደማትካፈል ትራምፕ በይፋ አስታወቁ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱአሜሪካ ደቡብ አፍሪካ በሚካሄደው የቡድን 20 ስብሰባ እንደማትካፈል ትራምፕ በይፋ አስታወቁ
አሜሪካ ደቡብ አፍሪካ በሚካሄደው የቡድን 20 ስብሰባ እንደማትካፈል ትራምፕ በይፋ አስታወቁ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 08.11.2025
ሰብስክራይብ

አሜሪካ ደቡብ አፍሪካ በሚካሄደው የቡድን 20 ስብሰባ እንደማትካፈል ትራምፕ በይፋ አስታወቁ

ዶናልድ ትራምፕ የደቡብ አፍሪካ ባለሥልጣናት የሀገሪቱን ነጭ ዜጎች መብት ይጥሳሉ በማለት ያቀረቡት ክስ ለውሳኔያቸው መነሻ እንደሆነ ገልፀዋል።

“ቡድን 20 በደቡብ አፍሪካ መካሄዱ እጅግ አሳፋሪ ነው” ሲሉ ፕሬዝዳንቱ በትሩዝ ሶሻል ማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ጽፈዋል።

“የደች፣ የፈረንሳይ እና የጀርመን ዝርያ ያላቸው 'አፍሪካነር' ሰፋሪዎች እየተገደሉና እየታረዱ እንዲሁም መሬታቸውና እርሻዎቻቸው በሕገ-ወጥ መንገድ እየተወረሱ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።

ትራምፕ በስብሰባው ላይ እንደማይገኙ ጥቅምት 26 አስቀድመው ገልጸው ነበር።

የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የነጭ ዜጎች የዘር ማጥፋት ክሱን የሚከላከል መግለጫ በምላሹ አውጥቷል። ሀገሪቱ አሜሪካ የአፍሪካነር ዝርያ ያላቸው የነጭ ደቡብ አፍሪካውያን የስደተኝነት ጥያቄዎችን ቅድሚያ ለመስጠት መወሰኗን ከዚህ በፊት ተችታለች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0