የሩሲያ እና የደቡብ አፍሪካ ጤና ጥበቃ ሚኒስትሮች በፕሪቶሪያ የሚገኘውን የኒውክሌር ህክምና ማዕከል ጎበኙ
10:41 08.11.2025 (የተሻሻለ: 10:44 08.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ እና የደቡብ አፍሪካ ጤና ጥበቃ ሚኒስትሮች በፕሪቶሪያ የሚገኘውን የኒውክሌር ህክምና ማዕከል ጎበኙ
ሚካሂል ሙራሽኮ እና አሮን ሞትሶአሌዲ በስቲቭ ቢኮ አካዳሚክ ሆስፒታል የሚገኘውን የኑሜሪ ማዕከል በጎበኙበት ወቅት የኒውክሌር ህክምና የጋራ ፍላጎት ቁልፍ ዘርፍ መሆኑን መግለፃቸውን የደቡብ አፍሪካ ጤና ሚኒስቴር ተወካይ ተናግረዋል፡፡
ተወካዩ እንዳሉት ሚኒስትሮቹ በጤና ስርዓቶች ውስጥ የምርመራ እና የህክምና አቅሞችን ለማጠናከር ያለውን አቅም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
እንደ ተወካዩ ገለጻ ሚኒስትሮቹ፡-
የላቁ የህክምና ቴክኖሎጂዎችን ጨምሮ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑን አስረግጠዋል፡፡
ለኒውክሌር ህክምና እና ለጋራ ምርምር ትስስር አቅም ግንባታ ልዩ ትኩረት በመስጠት ዋና ዋና የትብብር ጉዳዮችን ተወያይተዋል፡፡
ደቡብ አፍሪካ በመስከረም ወር በሩሲያ ልዑካን ቡድኗ የተሳተፈችበትን የኒውክሌር ህክምና ጉባኤ ለወደፊት ትብብር እንደ አስፈላጊ መድረክ ተመልክታዋለች ሲሉ ተወካዩ ገልፀዋል።
ኑሜሪ በኒውክሌር ህክምና እና እንደ ካንሰር ያሉ በሽታዎችን በማከም ረገድ አገልግሎት የሚሰጥ የምርምር ማዕከል ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X