ግብፅ በሕገ-ወጥ መንገድ የተዘረፉ 36 ቅርሶችን ከአሜሪካ አስመለሰች
20:23 07.11.2025 (የተሻሻለ: 20:34 07.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ግብፅ በሕገ-ወጥ መንገድ የተዘረፉ 36 ቅርሶችን ከአሜሪካ አስመለሰች
የቅርሶቹ መመለስ ግብፅ ቅርስዋን ለመጠበቅ ያላትን ጠንካራ ቁርጠኝነት ያሳያል ሲሉ የቱሪዝም ሚኒስትሩ ሸሪፍ ፋቲ ተናግረዋል።
የሮማውያን ዘመን ዕቃዎችን፣ 24 ብርቅዬ የእጅ ጽሑፎችን እና የ18ኛው ሥርወ መንግሥት ዘመን ባለቀለም የፕላስተር ፓኔልን ያካተቱ ሲሆን በታህሪር አደባባይ በሚገኘው የግብፅ ሙዚየም ለእይታ ይቀርባሉ ተብሏል።
በግብፅ እና በአሜሪካ ተቋማት መካከል ያለውን ውጤታማ ትብብር ያደነቁት ሚኒስትሩ፤ ሕገ-ወጥ የባሕልና የአርኪኦሎጂ ቅርስ ንግዶችን የመዋጋት አስፈላጊነት ዓለም አቀፍ እውቅና እያገኘ መምጣቱን ያሳያል ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X



