በክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም እስካሁን ከ80 በላይ ቴክኖሎጂዎች መመረታቸው ተገለፀ
16:44 07.11.2025 (የተሻሻለ: 16:54 07.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም እስካሁን ከ80 በላይ ቴክኖሎጂዎች መመረታቸው ተገለፀ
በፕሮጀክቱ ሥር የተካተቱ ከ500 በላይ ወጣቶች ተኪ ምርቶችን እና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በሀገር ውስጥ እያመረቱ እንደሚገኙ የፕሮግራሙ አስተባባሪ ብሩክ ሰለሞን ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል፡፡
በክህሎት ኢትዮጵያ ሁለተኛ ዙር በተኪ ምርቶች ላይ 152 ወጣቶች 99 ቴክኖሎጂዎችን እያለሙ ነው ብለዋል። በፕሮግራሙ ስር ግብርና፣ ጤና፣ ደህንነት እና አገልግሎትን የሚያሻሽሉ ቴክኖሎጂዎች መሠራታቸውንም ተናግረዋል።
ወጣቶቹ ካበለፀጓቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች መካከል፦
◻ የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ፣
◻ የግብርናና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በሮቦት በመታገዝ ማከናወን የሚያስችል ቴክኖሎጂ፣
◻ የፕላስቲክ ምርቶች ማምረቻ መሳሪያ እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡
የፕሮግራሙ አስተባባሪ በኢትዮጵያዊያን የተመረቱ ቴክኖሎጂዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ በተካሄዱ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውድድሮች ላይ ተሸላሚ መሆን መቻላቸውንም አስታውሰዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X