ለአፍሪካ የመንቂያ ጊዜው አሁን ነው - የዛምቢያ ብዊል ሕዝብ ንጉስ

ሰብስክራይብ

ለአፍሪካ የመንቂያ ጊዜው አሁን ነው - የዛምቢያ ብዊል ሕዝብ ንጉስ

ከፍተኛ አለቃ ፑታ ስምንተኛ፤ የአፍሪካ ሀገራት የእጅ አዙር የቅኝ ግዛት አካሄዶችን በጋራ በመመከት ሉዓላዊነታቸውን በምልዐት ማረጋገጥ እንዳለባቸው ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

"አንድ ከሆንን እንቆማለን፤ ከተከፋፈልን ደግሞ እንወድቃለን። በቀድሞ ዘመን እንደነበረው ሁኔታ ዳግም መገዛት አንፈልግም። አሁን ያለችው አፍሪካ በብዙ መልኩ የተለየች መሆኗን መረዳት ይገባል" ብለዋል።

ንጉሱ አፍሪካ ታሪኳን እና ማኅበራዊ እውነታዋን መሠረት በማድረግ የዘመኑን የሥልጣኔ ትርጉም ዳግም መበየን አንዳለባትም አስገንዝበዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0