ሩሲያ የዩናይትድ ስቴትስ እና ናይጄሪያን ግንኙነት እየተከታተለች ነው፤ ዓለም አቀፍ ሕግ እንዲከበር ታሳስባለች - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
13:51 07.11.2025 (የተሻሻለ: 13:54 07.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ የዩናይትድ ስቴትስ እና ናይጄሪያን ግንኙነት እየተከታተለች ነው፤ ዓለም አቀፍ ሕግ እንዲከበር ታሳስባለች - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
የናይጄሪያ ባለሥልጣናት ክርስቲያኖችን ከአሸባሪዎች ጥቃት መከላከል አልቻሉም በሚል የሚቀረበባቸውን ክስ ውድቅ ቢያደርጉም፤ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሀገሪቱ እና በመላው ዓለም የሚገኙ ክርስቲያኖችን ለመጠበቅ ዝግጁ መሆናቸውን ሐሙስ ዕለት በድጋሚ ገልጸዋል።
ትራምፕ ወታደሮችን ወደ ናይጄሪያ መላክ አሊያም በሀገሪቱ ላይ የአየር ጥቃቶችን መፈፀም ከጨዋታ ውጪ እንዳልሆነ ሰኞ ዕለት ተናግረዋል። የአሜሪካ አስተዳደር በናይጄሪያ የተነጣጠሩ የድሮን ጥቃቶችን የማካሄድ እና ለምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር የሚሰጠውን እርዳታ የማገድ ዕቅድ ላይ እያጤነ እንደሆነ ቀደም ሲል የመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች አመልክተዋል።
የፔንታጎን ኃላፊ ፒት ሄግሴዝ ፕሬዝዳንት ትራምፕ የሰጡትን ትዕዛዝ ተከትሎ የጦር ሚኒስቴሩ ናይጄሪያ ውስጥ በሚገኙ እስላማዊ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ ለመውሰድ እየተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X