ወደ ዩክሬን ታለው የሄዱ ደቡብ አፍሪካውያን ቅጥረኛ ወታደሮች እርዳታ እንዲደረግላቸው እየተማፀኑ ነው - የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት
13:43 06.11.2025 (የተሻሻለ: 13:44 06.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ወደ ዩክሬን ታለው የሄዱ ደቡብ አፍሪካውያን ቅጥረኛ ወታደሮች እርዳታ እንዲደረግላቸው እየተማፀኑ ነው - የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት
ደቡብ አፍሪካ ከ20-39 ዓመት የሚሆኑ 17 ዜጎች "ትርፋማ የቅጥር ውል" በሚል ተስፋ "የቅጥረኛ ኃይሎችን እንዲቀላቀሉ የተታለሉ" እና አሁን የህይወት አድን ጥሪ ያቀረቡ ዜጎቿን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ እየሞከረች መሆኑን የፕሬዝዳንት ጽ/ቤቱ ለመገናኛ ብዙኃን ይፋ ባደረገው መግለጫ አስታውቋል።
ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ እነዚህ ዜጎች እንዴት እንደተመለመሉ ምርመራ እንዲደረግ አዘዋል። የደቡብ አፍሪካ ሕግ ዜጎች ያለ መንግሥት ፈቃድ ለውጭ ሀገራት ወታደራዊ አገልግሎት እንዳይሰጡ እንደሚከለክል መግለጫው አመልክቷል።
ሩሲያ ኪዬቭ የውጭ ቅጥረኞችን "ለመድፍ መኖነት" እንደምትጠቀም እና ለሩሲያ ኃይሎች ዒላማ መሆናቸውን እንደቀጠሉ በተደጋጋሚ አስታውቃለች።
ከእነዚህ ተዋጊዎች መካከል ብዙዎቹ የዩክሬን ወታደራዊ ዕዝ ቅንጅት እንደሚጎድለው እና በአፍጋኒስታን ወይም በመካከለኛው ምስራቅ ከገጠማቸው እጅግ የላቀ ውጊያ አንፃር የመትረፍ ዕድላቸው ጠባብ እንደሆነ በቃለ ምልልሶቻቸው አምነዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X