ኢትዮጵያ የብሪክስ የቱሪዝም አካዳሚ ማዕከል ለመሆን ፕሮፖዛል አቅርባለች - የቱሪዝም ሚኒስቴር

ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ የብሪክስ የቱሪዝም አካዳሚ ማዕከል ለመሆን ፕሮፖዛል አቅርባለች - የቱሪዝም ሚኒስቴር

አካዳሚው ለዓለም አቀፍ ተማሪዎች በሆቴል እና ቱሪዝም ዘርፍ ልዩ ትምህርት እና ሥልጠና እንዲሰጥ መታቀዱንም የቱሪዝም ሚኒስትር ዴዔታ ስለሺ ግርማ ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልፀዋል።

ሀገሪቱ ብሪክስ ካለው ሰፊ የሕዝብ ብዛት እና ጠንካራ ኢኮኖሚ በቱሪዝም ዘርፉ ተጠቃሚ ለመሆን እየሠራች መሆኑን አመላክተዋል።

"እንደ ሩሲያ እና ቻይና ያሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑ ሀገራትን ያቀፈው ብሪክስ አንድ ሦስተኛው የሚሆነውን የዓለም ሕዝብ ይዟል። ይህ ሰፊ ሕዝብ ለሀገሪቱ ቱሪዝም ከፍተኛ ዕድል ነው" ብለዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0