ባለፉት ሦስት ወራት ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ የዓሣ ምርት 704 ሚሊዮን ብር መገኘቱ ተገለፀ
11:36 05.11.2025 (የተሻሻለ: 11:44 05.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ባለፉት ሦስት ወራት ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ የዓሣ ምርት 704 ሚሊዮን ብር መገኘቱ ተገለፀ
በመጀመሪያው ሩብ ዓመት 1,408 ቶን ዓሣ በማምረት ይህ ገቢ መገኘቱን የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ አስታውቋል፡፡
የተገኘው ምርት ለ2018 በጀት ዓመት የተቀመጠውን የ9,655 ቶን ግብ ለማሳካት ትልቅ እርምጃ መሆኑ ተገልጿል።
በቀጣይ ወራት የዓሣ ምርትን ለማሳደግ አዳዲስ ተነሳሽነቶች እየተተገበሩ መሆኑን ቢሮው ጠቁመዋል።
የግብርና ሚኒስቴር በግድቡ አማካኝነትን የተፈጠረውን የንጋት ሐይቅ ደህንነት እና የዓሣ ሀብት አጠቃቀም ማስተዳደር የሚያስችል መመሪያ ማዘጋጀቱን መግለፁ የሚታወስ ነው፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X