በአሜሪካ የቀረበው ጋዛን 'የሚያረጋጋት ኃይል' ላይ የተመድ ሥልጣን ሊኖረው ይገባል ሲሉ የድርጅቱ ዋና ጸሐፊ ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበአሜሪካ የቀረበው ጋዛን 'የሚያረጋጋት ኃይል' ላይ የተመድ ሥልጣን ሊኖረው ይገባል ሲሉ የድርጅቱ ዋና ጸሐፊ ተናገሩ
በአሜሪካ የቀረበው ጋዛን 'የሚያረጋጋት ኃይል' ላይ የተመድ ሥልጣን ሊኖረው ይገባል ሲሉ የድርጅቱ ዋና ጸሐፊ ተናገሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 04.11.2025
ሰብስክራይብ

በአሜሪካ የቀረበው ጋዛን 'የሚያረጋጋት ኃይል' ላይ የተመድ ሥልጣን ሊኖረው ይገባል ሲሉ የድርጅቱ ዋና ጸሐፊ ተናገሩ

ከጦርነቱ በኋላ ያለው የሽግግር ጊዜ በጋዛ ሰርጥ ውስጥ ያለውን ሙሉ ሥልጣን ወደ ፍልስጤም አስተዳደር እንዲሸጋገር ማድረግ አለበት፤ ሲሉ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ   በዓለም አቀፍ የማኅበራዊ ልማት ጉባኤ ጎን ለጎን ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡

አሜሪካ ለበርካታ የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት አባላት በትንሹ ለሁለት ዓመታት በጋዛ ውስጥ የዓለም አቀፍ የደህንነት ኃይሎችን ለመፍጠር የሚያስችል ረቂቅ የውሳኔ ሐሳብ ልካለች፤ ሲል የአሜሪካ ኒውስ ፖርታል እጁ የገባውን የሰነድ ግልባጭ በመጥቀስ ቀደም ብሎ ዘግቧል።

የታቀደው ዓለም አቀፍ የደህንነት ኃይል ከኢንዶኔዢያ፣ አዘርባጃን፣ ግብፅ እና ቱርክ የሚውጣጣ ሲሆን ዶናልድ ትራምፕ በሊቀ-መንበርነት በሚመሩት "የሰላም ቦርድ" ስር እንደሚንቀሳቀስ ሕትመቱ አመልክቷል።

የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ድርድርን ተከትሎ ኃይሉ ጥር ወር ውስጥ እንዲሰማራ መታቀዱን  ዘገባው አመልክቷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0