የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የ'ኒውክለር ሪአክተር' የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሠራ ነው ተባለ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የ'ኒውክለር ሪአክተር' የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሠራ ነው ተባለ
የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የ'ኒውክለር ሪአክተር' የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሠራ ነው ተባለ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 04.11.2025
ሰብስክራይብ

የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የ'ኒውክለር ሪአክተር' የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሠራ ነው ተባለ 

በዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት አብርሃም ደበበ (ዶ/ር)፣ የኒውክለር ጣቢያ ለመገንባት መታቀዱና የኢትዮጵያ ኒውክሌር ኃይል ኮሚሽን መቋቋም ዩኒቨርሲቲው እያከናወነ ላለው ተግባር ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ለአገር ውስጥ ሚዲያ አስረድተዋል።

ዩኒቨርሲቲው ባለፉት ስምንት ዓመታት በዘርፉ ሲሰራ የቆየ ሲሆን፦

▪ ዩኒቨርሲቲው ካሉት ስምንት የልህቀት ማዕከላት የኒውክለር ሪአክተር ቴክኖሎጂ አንዱ ነው።

▪ ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ተማሪዎችን በማስተርስ መርሃ ግብር እያስተማረ ይገኛል።

▪ የዩኒቨርሲቲው የኒውክለር ሪአክተር ቴክኖሎጂ ልህቀት ማዕከል ሕንፃ ግንባታ ተጠናቅቋል።

▪ የላቦራቶሪ ዕቃዎችን ለማሟላት ከሚመለከተው አካል ጋር እየተሠራ ነው።

የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ተመስገን ወንድሙ (ዶ/ር)፣ በበኩላቸው “ዩኒቨርሲቲው ለኢትዮጵያ ኒውክሌር ኃይል ኮሚሽን (በመቋቋም ላይ የሚገኘው) አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የኑክሌር ልማት ፕሮጀክት ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0