ማሊ ሁለተኛውን የሊቲየም ማዕድን ማውጫ በዛሬው ዕለት ማስመረቋን የፕሬዝደንቱ ቢሮ አስታወቀ

ማሊ ሁለተኛውን የሊቲየም ማዕድን ማውጫ በዛሬው ዕለት ማስመረቋን የፕሬዝደንቱ ቢሮ አስታወቀ
የሽግግሩ ፕሬዝደንት አሲሚ ጎይታ የምረቃ ሥነ-ሥረአቱን መርተዋል ሲል ቢሮው ጨምሮ አስታውቋል።
ማዕድን ማውጫውን አስመልክቶ የተገለፁ ዋና ዋና ነጥቦች ፦
🟠 ማዕድኑ የሚገኘው በቡጉኒ ክልል ሲሆን፣ በየዓመቱ 400 ሺህ ቶን የሊቲየም ክምችት ያመርታል ተብሎ ይጠበቃል። ይህም ማሊን ከአፍሪካ የምርቱ ከፍተኛ ወሳኝ ብረት አምራቾች አንዷ ያደርጋታል።
🟠 እንደ ክሮዋሳንስ ማሊ ዘገባ፤ የማዕድን ማውጫው ኦፕሬተር የሆነው "ሊቲየም ማይንስ ኦፍ ቡጉኒ"፤ 65 በመቶ በብሪታኒያ የተመሠረተው ኮዳል ማይኒንግ እና 35 በመቶው ደግሞ በማሊ መንግስት ባለቤትነት ስር ነው።
🟠 ፕሮጀክቱ 250 ሚሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንትን ይወክላል።
🟠 በሺዎች ለሚቆጠሩ የማሊ ዜጎች ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆኑ የሥራ ዕድሎችን ፈጥሯል።
የአፍሪካ ግዙፉ የማዕድን ማውጫ እንደሆነ የሚታሰበው እና በቡጉኒ ክልል የሚገኘው የማሊ የመጀመሪያው የሊቲየም ማዕድን ማውጫ ጉላሚና ተብሎ የሚጠራ ሲሆን በ2017 ዓ.ም አጋማሽ ላይ ወደ ስራ ገብቷል።
ℹ ሊቲየም በአሁኑ ወቅት ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ባትሪዎች፣ ለቀጣይ ትውልድ (next-generation) ተሽከርካሪዎች እና ለዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎች ምርት ወሳኝ የሆነ ስትራቴጂያዊ ብረት ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X


