የሩሲያ-አላስካ መተላለፊያ ርዝመት ይፋ ተደረገ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየሩሲያ-አላስካ መተላለፊያ ርዝመት ይፋ ተደረገ
የሩሲያ-አላስካ መተላለፊያ ርዝመት ይፋ ተደረገ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 03.11.2025
ሰብስክራይብ

የሩሲያ-አላስካ መተላለፊያ ርዝመት ይፋ ተደረገ 

የወደፊቱ መተላለፊያ (ዋሻ) አጠቃላይ ርዝመት ከ98 እስከ 112 ኪሎ ሜትር ሊደርስ ይችላል ሲሉ የፕሮጀክቱ ኃላፊ እና መሪ ተመራማሪ ቪክቶር ራዝቤጊን ተናግረዋል፡፡

ራዝበጊን ሲያብራሩ፡- “ሁለት ባሕሮችን (ውሃዎችን) የሚገናኝኘው መስመር ዝቅተኛ ስፋት 83 ኪሎ ሜትር አካባቢ ነው። ሆኖም፣ መውጫዎቹንም ግምት ውስጥ ማስገባት አለብን፡፡  መሃል ላይ  ራትማኖቭ እና ክሩሰንስተርን ተብለው የሚጠሩ ሁለት ደሴቶች ስላሉ የሚገነባው መስመር በቀጥታ አልተሳለም። በደሴቶቹ መካከል ያለው ርቀት 4.5 ኪሎ ሜትር ብቻ ስለሆነ ለግንባታ ምቹ ያደርጋቸዋል። ስለዚህ በእነዚህ ደሴቶች በኩል የሚያልፈው መስመር እንደ ፕሮጀክቱ ስሪት ከ98 እስከ 112 ኪሎ ሜትር ይለያያል” ብለዋል።

ሳይንቲስቱ የሁለቱ ደሴቶች መኖር ለንድፉ ቁልፍ ነገር መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል፡፡ ይህም ዋሻው ሦስት ክፍሎች ሊኖሩት ይችላል፤ ማለትም፣  በደሴቶቹ መካከል ያለው ትንሽ ክፍል (4.5 ኪሜ) እና የሁለቱ ትላልቅ ክፍሎች የእያንዳንዳቸው ርዝመት በፈረንሳይና በእንግሊዝ መካከል ካሉት "ቻናል ተነል" መተላለፊያ ጋር የሚወዳደሩ ይሆናሉ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0