በዲጂታል ክፍያ ከ17 ትሪሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ዝውውር ሲፈፀም በሞባይል ባንኪንግ 76% በላይ ድርሻ መያዙ ተዘገበ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበዲጂታል ክፍያ ከ17 ትሪሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ዝውውር ሲፈፀም በሞባይል ባንኪንግ 76% በላይ ድርሻ መያዙ ተዘገበ
በዲጂታል ክፍያ ከ17 ትሪሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ዝውውር ሲፈፀም በሞባይል ባንኪንግ 76% በላይ ድርሻ መያዙ ተዘገበ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 02.11.2025
ሰብስክራይብ

በዲጂታል ክፍያ ከ17 ትሪሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ዝውውር ሲፈፀም በሞባይል ባንኪንግ 76% በላይ ድርሻ መያዙ ተዘገበ

በ2017 የበጀት ዓመት አፈጻጸም ከቀዳሚው ዓመት በእጥፍ እንደሚበልጥ ተጠቁሟል።

በ2016 በሞባይል ባንኪንግ የተንቀሳቀሰው 6.71 ትሪሊዮን ብር በ2017 ወደ ከ13.1 ትሪሊዮን ብር አድጓል፡፡

ሚዲያው ኢት-ስዊች አክሲዮን ማኅበርን ዋቢ አድርጎ በበጀት ዓመቱ ዋና ዋና ያላቸውን የዲጂታል ገንዘብ ግኝቶች እንደሚከተለው አጋርቷል፦

በሞባይል ዋሌት አማካኝነት 2.08 ትሪሊዮን ብር የገንዘብ ዝውውር ተደርጓል (የእጥፍ ጭማሪ አለው)።

በኢንተርኔት አማካኝነት 1.7 ትሪሊዮን ብር ተንቀሳቅሷል።

በኤትኤም 729.8 ቢሊዮን ብር ሲንቀሳቀስ ካለፈው የበጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር ብዙ ዕደገት አላሳየም።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መረጃን ዋቢ ያደረገው የአገር ውስጥ የግል ሚዲያ፣ የሞባይል ባንክ የገንዘብ ዝውውር ከኤትኤምና ከፖስ (PoS) አንጻር ከፍተኛ ደረጃ ዕድገት እያሳየ ነው ብሏል፡፡

በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለጸገ ምስል

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0