ትራምፕ ክርስትያኖች እየተሰደዱ ነው በሚል ክስ ናይጄሪያን 'ልዩ ስጋት ያለባት ሀገር' ብለው ፈረጁ
19:37 01.11.2025 (የተሻሻለ: 20:04 01.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ትራምፕ ክርስትያኖች እየተሰደዱ ነው በሚል ክስ ናይጄሪያን 'ልዩ ስጋት ያለባት ሀገር' ብለው ፈረጁ
ይህ ውሳኔ የመጣው በአሜሪካና በአውሮፓ ያሉ ወግ አጥባቂ ግለሰቦች በናይጄሪያ የክርስትያኖች የዘር ማጥፋት ወንጀል እየተፈጸመ ነው የሚል ክስ በዘመቻ ካቀረቡ በኋላ ነው።
ትራምፕ ራሳቸው ሁኔታውን ለማሻሻል ትኩረት እንደሰጡ ገልጸው፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ክርስትያኖች በ"ጽንፈኛ እስላማውያን" ተገድለዋልና ክርስትና የሕልውና አደጋ እንደገጠመው አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል፣ የናይጄሪያ መንግሥት የሀገሪቱን የጸጥታ ችግሮች እውቅና ቢሰጥም፣ ክርስትያኖች በተለየ መልኩ ዒላማ እንዳልሆኑ ገልጿል። መንግሥት ችግሮቹ እየተፈቱ መሆናቸውንም አክሏል።
የመረጃ ሚኒስትር ሞሐመድ ኢድሪስ ናይጄሪያ ሁሉንም አይነት የጸጥታ ችግሮች በጋራ የምትዋጋ፤ የብዝኃ ሐይማኖቶች ሀገር እንደሆነች መረዳት እና ማክበር እንደሚገባ አሳስበዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X