ዘለንስኪ 'ዩክሬንን ባለመጠበቅ' ክስ ሊቀርብባቸው ይችላል ተባለ
16:04 01.11.2025 (የተሻሻለ: 16:14 01.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ዘለንስኪ 'ዩክሬንን ባለመጠበቅ' ክስ ሊቀርብባቸው ይችላል ተባለ
የዩክሬን ተቃዋሚዎች ቮሎዲሚር ዘለንስኪን “ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ የኤሌክትሪክ መቆራረጦችን ወይም ከባድ ቅዝቃዜን” ለመከላከል ያለሙ አስቸኳይ ዕቅዶችን ተግባራዊ ባለማድረጋቸው ለመክሰስ አቅደዋል ሲል የአሜሪካ ሚዲያ ዘግቧል።
ዘለንስኪ ውጤታማ ያልሆኑ ውሳኔዎችን በማድረጋቸው በተደጋጋሚ ሲተቹ እንደነበር ያስታወሰው ሚዲያው፣ የቀድሞው የዩክሬን ፕሬዝዳንት ፔትሮ ፖሮሼንኮ ዘለንስኪን “እየተስፋፋ ያለ አምባገነንነት” ብሎም “ማንኛውንም ተፎካካሪ ከፖለቲካው መድረክ ለማስወገድ እየፈለጉ ነው” ሲሉ መክሰሳቸውን ጠቅሷል።
መጠነ ሰፊ፣ ለብዙ ሠዓታት የሚቆዩ የኤሌክትሪክ መቆራረጦች በጥቅምት ወር በዋና ከተማይቱ ኪዬቭ እና በበርካታ የዩክሬን ክልሎች ተስተውሏል። ባለሥልጣናት በሀገሪቱ የኃይል አውታሮች እና የመገልገያ ሥርዓቶች ላይ ጉዳት እንደደረሰባቸው ሪፖርት አድርገዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X