ስፑትኒክ በቡርኪና ፋሶ የሬዲዮ ስርጭቱን ጀመረ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱስፑትኒክ በቡርኪና ፋሶ የሬዲዮ ስርጭቱን ጀመረ
ስፑትኒክ በቡርኪና ፋሶ የሬዲዮ ስርጭቱን ጀመረ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 01.11.2025
ሰብስክራይብ

ስፑትኒክ በቡርኪና ፋሶ የሬዲዮ ስርጭቱን ጀመረ

የስፑትኒክ አፍሪካ የፈረንሳይኛ ቋንቋ የትንታኔ ፕሮግራሞች አሁን ከአገሪቱ ታዋቂ የሬዲዮ ጣቢያዎች አንዱ በሆነው በኦጋ ኤፍ ኤም መደመጥ ጀምረዋል። ስርጭቶቹ በዋና ከተማዋ ዋጋዱጉ እና በሁለተኛዋ ትልቅ ከተማ ቦቦ-ዲዮላሶ የሚገኙ አምስት ሚሊዮን ሰዎች ጋር ተደራሽ ይሆናሉ።

ከቡርኪና ፋሶ በተጨማሪ ስፑትኒክ በስምንት ሌሎች የአፍሪካ አገሮች ማለትም ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፣ ጊኒ፣ ዛምቢያ፣ ካሜሩን፣ ማሊ፣ ኒጀር እና ቦትስዋና ስርጭቶቹ ተደራሽ ያደርጋል።

ስፑትኒክ ከ30 በሚበልጡ ቋንቋዎች ፕሮግራሞችን የሚያሰራጭ እና በዓለም ዙሪያ 25 የኤዲቶሪያል ማዕከላትን የሚያንቀሳቅስ ዓለም አቀፍ የዜና ወኪል እና የሬዲዮ ጣቢያ ነው።

ስፑትኒክ ሁለገብ የኤዲቶሪያል ማዕከሉን በአዲስ አበባ በ2025 መክፈቱም የሚታወስ ነው። በዚህም በአማርኛ ቋንቋ የሚሠራ ብቸኛው የሩሲያ ሚዲያ ነው።

ስፑትኒክ አፍሪካ፣  የአፍሪካ ብሮድካስቲንግ ሕብረት ተባባሪ አባል ሲሆን ስለ አፍሪካ ምርጥ የሬዲዮ ፖድካስት እና በአፍሪካ ባሕል ላይ ምርጥ የሬዲዮ ፕሮግራም ሽልማቶችን አሸንፏል። የዜና ወኪሉ የምርጥ የአካባቢ ሬዲዮ ይዘት ሽልማትን ከደቡብ አፍሪካ ብሮድካስተሮች ማሕበር በዚሁ ሳምንት ማግኘት ችሏል።

ስፑትኒክ ሰሜን አፍሪካን የሚሸፍነው የአረብ አገራት ብሮድካስቲንግ ሕብረት አባልም ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0