በሩሲያ እና በአፍሪካ መካከል እየጨመረ ያለው የንግድ ልውውጥ 27 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል - የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
15:20 01.11.2025 (የተሻሻለ: 15:24 01.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በሩሲያ እና በአፍሪካ መካከል እየጨመረ ያለው የንግድ ልውውጥ 27 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል - የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
በሚኒስቴሩ የአፍሪካ አጋርነት መምሪያ ኃላፊ ታቲያና ዶቭጋሌንኮ በጋራ ውይይት ወቅት የሰጧቸው ተጨማሪ መግለጫዎች፦
በተፈጥሮ ሀብት ዘርፍ ትብብር ያለው የሩሲያ-አፍሪካ ውይይት ማዕከላዊ ምሰሶ ነው፤
ሩሲያ፣ የአፍሪካ የረጅም ጊዜ ወዳጅ እንደመሆኗ፣ ከፖለቲካዊ ቅኝ ግዛት ነጻ መውጣት በኋላ የኢኮኖሚ፣ የቴክኖሎጂ እና የኃይል ሉዓላዊነት እንዲሳካ ትደግፋለች፡፡
የሩሲያ ኩባንያዎች እንደ ናይጄሪያ የሚገኘውን የአጃኦኩታ ብረታ ብረት ኮምፕሌክስን መልሶ ማቋቋም እና በግብፅ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ግንባታ ባሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶች ላይ ተሳትፈዋል፡፡
እ.ኤ.አ. በ2019 ከመጀመሪያው የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ወዲህ በሩሲያ የሚገኙ የአፍሪካ ተማሪዎች ቁጥር እጥፍ ሊጠጋ ቀርቦ 32 ሺህ ደርሷል፡፡ በዩኒቨርሲቲዎች መካከል ከ800 በላይ ስምምነቶች ተፈርመዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለጸገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X