የታንዛኒያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫን ሳሚያ ሀሰን ማሸነፋቸውን የሀገሪቱ ምርጫ ኮሚሽን አረጋገጠ
14:16 01.11.2025 (የተሻሻለ: 14:24 01.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የታንዛኒያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫን ሳሚያ ሀሰን ማሸነፋቸውን የሀገሪቱ ምርጫ ኮሚሽን አረጋገጠ
ሳሚያ ሀሰን ከ31.9 ሚሊዮን በላይ ድምጾችን በማግኘት፣ ከተሰጡት ድምጾች 97.66 በመቶ ማስመዝገባቸውን የምርጫ ኮሚሽኑ አስታውቋል።
ከተመዘገቡት 37.6 ሚሊዮን መራጮች መካከል 87 በመቶ የሚጠጉት ድምጽ ሰጥተዋል ተብሏል።
የምርጫ ኮሚሽኑ በሥልጣን ላይ ያሉት ፕሬዝዳንት ሁለት ዋና ተፎካካሪዎችን አግልሏል፤ በፕሬዝዳንታዊና የፓርላማ ምርጫ ወቅት ጭቆና ተፈጽሟል በሚል ረቡዕ እለት ተቃውሞዎች መቀስቀሳቸውን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
የታንዛኒያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማሕሙድ ታቢት ፣ የጸጥታ ኃይሎች ከመጠን ያለፈ እርምጃ አልወሰዱም፤ ከወንጀል ጉዳዮች ጋር የተያያዙ "በጣም ጥቂት መጠነኛ ክስተቶች" ብቻ ነበሩ ሲሉ ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X