“ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር አስተዳደር ውስጥ ምንም ዓይነት ሚና የላትም” - የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
20:27 31.10.2025 (የተሻሻለ: 20:34 31.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
“ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር አስተዳደር ውስጥ ምንም ዓይነት ሚና የላትም” - የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
“የቀይ ባሕርን የማስተዳደር ጉዳይ የባሕር ዳርቻ ሀገራትን ብቻ የሚመለከት ነው” ሲሉ ባድር አብደላቲ ለአል አረቢያ ተናግረዋል።
እንደ ኢትዮጵያ ያሉ የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት ተሳትፎ “ተቀባይነት የለውም” ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል።
ግብፅ ከሳዑዲ አረቢያ ጋር በቀይ ባሕር አስተዳደር የወደፊት እጣ ፈንታ ዙሪያ እየመከረች መሆኑን የገለፁት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ “ይህን ወሳኝ የባሕር ላይ መተላለፊያ የማስተዳደር፣ ደህንነቱንና መረጋጋቱን የማረጋገጥ ቀዳሚ ኃላፊነት ያለባቸው” ሁለቱ ሀገራት ናቸው ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ኢትዮጵያ የባሕር በር መነፈጓን እንደማትቀበል እና ስትራቴጂካዊ ጥቅሞቿን በሰላማዊ መንገድ ለማስከበር ቁርጠኛ መሆኗን በሳምንቱ መጀመሪያ መግለፃቸው ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X