የንጋት ሐይቅን ደህንነት እና ሀብት አጠቃቀም ማስተዳደር የሚያስችል መመሪያ መዘጋጀቱ ተገለፀ
17:07 31.10.2025  (የተሻሻለ: 17:14 31.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
 / ሰብስክራይብ
የንጋት ሐይቅን ደህንነት እና ሀብት አጠቃቀም ማስተዳደር የሚያስችል መመሪያ መዘጋጀቱ ተገለፀ
ሰነዱ የሕዳሴ ግድብ ሐይቅን ከተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ ችግሮች ለመከላከል እና በውስጡ ያለውን የዓሳ ሃብት በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችል ሆኖ መዘጋጀቱን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
በመመሪያው የተካተቱ ዝርዝር ጉዳዮች፦
ዓሣ የማስገር ሂደት፣
የዝርያ ማሻሻያ ሥራዎች፣
የዓሣ መረብ አጠቃቀምን ማሻሻል፣
የገበያ ትስስር መፍጠር፡፡
ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና የምርምር ማዕከላት በመመሪያው አተገባበር ዙሪያ በጥናት የተደገፈ ግብዓት እንዲያቀርቡ አቅጣጫ መቀመጡንም ጠቅሰዋል፡፡
ንጋት ሐይቅ በአሁኑ ወቅት 15 ሺህ ቶን ዓሣ የማምረት አቅም ያለው ሲሆን በዓሣ ማስገር ሥራ በተሠማሩ 78 ማህበራት ውስጥ አባላት ለሆኑ ከ866 በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች የሥራ እድል ፈጥሯል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X