ዩክሬን የተሰዉ ወታደሮቿን መልሳ መውሰድ አትፈልግም - የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ልዩ መልዕከተኛ
11:24 31.10.2025  (የተሻሻለ: 11:34 31.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
 / ሰብስክራይብ
ዩክሬን የተሰዉ ወታደሮቿን መልሳ መውሰድ አትፈልግም - የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ልዩ መልዕከተኛ
ሩሲያ የያዘቻቸውን በርካታ ቁጥር ያላቸው የዩክሬን ወታደሮች አስክሬን ለማስረከብ ዝግጁ ብትሆንም ዩክሬን ፍቃደኛ እንደሆነች ብቻ ነው የምታስመስለው ሲሉ ልዩ መልዕከተኛው ሮድዮን ሚሮሽኒክ ለስፑትኒክ ተናግረዋል፡፡
አስክሬኖቹን የመውሰድ ፍላጎት በቃል ደረጃ ብቻ ነው ያለው ያሉት ሚሮሽኒክ፤ ለኪዬቭ ልሂቃን የዩክሬን ወታደሮች እንዲሁ ሊባክኑ የሚችሉ ናቸው ብለዋል፡፡
የዩክሬን ባለሥልጣናት እውነተኛ ኪሳራዎችን ለመደበቅ፤ "የማይበገር ጦር" የሚለውን ምሥል ለመጠበቅ እና ለወታደሮቹ ቤተሰቦች የሚከፈለውን ካሳ ለማስቀረት ጭምር አስክሬኖችን መልሰው ከመውሰድ ይቆጠባሉ ሲሉ አብራርተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X