የኢትዮጵያ አየር መንገድ በናይጄሪያ ትልቁ ዓለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት አቅራቢ ሆነ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ አየር መንገድ በናይጄሪያ ትልቁ ዓለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት አቅራቢ ሆነ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በናይጄሪያ ትልቁ ዓለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት አቅራቢ ሆነ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 30.10.2025
ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በናይጄሪያ ትልቁ ዓለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት አቅራቢ ሆነ

አየር መንገዱ ከጥቅምት 18 ጀምሮ ከአቡጃ ወደ አዲስ አበባ ተጨማሪ ሶስት ሳምንታዊ የምሽት በረራዎችን በማስጀመር አጠቃላይ ቁጥሩን 34 አድርሷል።

“ናይጄሪያን ከ150 በላይ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች ጋር አገናኝተናል። ለዚህም ኤርባስ ኤ350-1000 እና ቦይንግ 787 ድሪምላይነርን ጨምሮ በዓለም ላይ ካሉት እጅግ ዘመናዊና አዳዲስ አውሮፕላኖች መካከል ቀዳሚዎቹን ተጠቅመናል” ሲሉ በናይጄሪያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሥራ አስኪያጅ ፍሬህይወት መኮንን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሁን ላይ፦

ወደ ሌጎስ፦ ሁለት ዕለታዊ እና 14 ሳምንታዊ በረራ፣

ወደ አቡጃ፦ 10 ሳምንታዊ በረራ፣

ወደ እኑጉ፦ ሶስት ሳምንታዊ በረራ፣

ወደ ካኖ፦ ሰባት ሳምንታዊ በረራ ያደርጋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ወደ ናይጄሪያ የመጀመሪያውን በረራ ያደረገው ከ65 ዓመታት በፊት በ1952 ነበር፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0