ኢትዮጵያ ለክሪፕቶ ማይኒንግ አዲስ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ይፋ አደረገች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ ለክሪፕቶ ማይኒንግ አዲስ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ይፋ አደረገች
ኢትዮጵያ ለክሪፕቶ ማይኒንግ አዲስ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ይፋ አደረገች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 30.10.2025
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ ለክሪፕቶ ማይኒንግ አዲስ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ይፋ አደረገች

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለዘርፉ ደንበኞች ከህዳር 22 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ የተሻሻለ ክፍያ ማዘጋጀቱን አስታውቋል።

አዲሱ ማሻሽያ፤ የጊዜ አጠቃቀም ሥርዓትን መሠረት ያደረገ የታሪፍ ማስተካከያ አሠራርን የሚዘረጋ ነው፡፡

የአጠቃቀም ሰዓቱ በሶስት የተዋቀረ ሲሆን፦

የከፍተኛ ፍጆታ ሰዓታት ከምሽቱ 12:00 እስከ ምሽቱ 4:00፤ ከ0.06 የአሜሪካ ዶላር ጀምሮ በከፍተኛ ዋጋ የሚሰላ፣

የመካከለኛ ፍጆታ ሰዓታት ከጠዋቱ 3:00 እስከ ምሽቱ 12:00፤ ከ0.035 የአሜሪካ ዶላር ጀምሮ የሚሰላ፣

የዝቅተኛ የፍጆታ ሰዓታት ከምሽቱ 5:00 እስከ ንጋቱ 11:00 ከ0.035 የአሜሪካ ዶላር ጀምሮ የሚሰላ፡፡

አዲሱ ታሪፍ እስከ ሐምሌ 2020 ዓ.ም ድረስ ዓመታዊ የዋጋ ጭማሪ እንደሚደረግበት ተቋሙ አስታወቋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፈው በጀት ዓመት ከአጠቃላይ ሽያጭ 18 በመቶውን ለዳታ ማይኒንግ ዘርፍ በማቅረብ፤ 220 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ስለማግኝቱ መግለፁ ይታወሳል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0